እምቅ የተፈጥሮ ፀጋዎች ለምተው የህብረተሰቡ ህይወት በተጨባጭ እንዲለወጥ እንሰራለን ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አመራሮች ገለፁ።
ክልሉ ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በመተባበር “በእውቀትና በክህሎት የተገነባ አመራር ለላቀ ውጤት ” በሚል መሪ ቃል ለከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው የአቅም ግንባታ ስልጠና 4ተኛ ቀኑን ይዟል።
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሚዲያ ጋር ቆይታ ያደረጉ የስልጠናው ተሳታፊ አመራሮች እንዳሉት በክልሉ ያሉ እምቅ የተፈጥሮ ፀጋዎች ለምተው የህብረተሰቡ ህይወት በተጨባጭ እንዲለወጥ የሚያስችል ስንቅ በስልጠናው አገኝተናል ብለዋል ።
በክልሉ “ፀጋዎች አሉን” ከማለት ያለፈ ተጨባጭ ስራ መስራት የአመራሮች ተቀዳሚ ተግባር መሆን እንደሚገባውም ገልፀዋል ።
ክልሉ በምድር የተሰጠውን በረከት መረዳትና እንዲለማ መትጋት ተቀዳሚ አጀንዳችን ነውም ብለዋል-አመራሮቹ።
አመራሮች የመሪነት ጥበብን በአሻጋሪ ሀሳብ ላይ ተመስርተን ከሰራን ተጠባቂ ዕድገት ማስመዝገብ እንችላለን ሲሉም አሳውቀዋል ።
ሁሉም የክልሉ ህዝቦች የሰላም እሴት ግንባታው ተጠናክሮ እንዲቀጥል መስራት ይገባልም ብለዋል ።
በተለይ የኢትዮጵያዊያን የመጪው ዘመን የብርሃን አቢዮት ፈንጣቂው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ይዞት የሚመጣውን ዘርፈ ብዙ በረከት በሚገባ ለመጠቀም ዝግጁ መሆን ከመሪዎች እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።


